Digital Leadership and Disruptive Technology: Managing Recor
Ethiopia Archives and Library Services, Ministry of Innovation and Technology, Balbbiys PLC, and Records Management Foundation for Africa (RMFA) are hosting the 40th RMFA Inte
የቤተመጻሕፍት ታሪክ የደግነት ታሪክ ነው ፡፡ ደጋግ ጸሐፍት በብዙ ትጋት ለአንክሮ፣ ለተዘክሮና ለአስተምህሮ የከተቡትን ክርታስ ሌሎች ደጋጎች በበኩላቸው ቤት ሰርተው ፣ መንበር አበጅተው ፣ ማቶት አብርተው ትውልዱ እንዲታደምላቸው ” እንካችኹ ይኽችን መጽሐፍ ብሉ ” ማለታቸው የሕብረተሰብ መሠረቱ ደግነት መኾኑን ያበስረናል ፡፡ የብሔራዊ ቤተመጻሕፍት ወመዘክርን ፸፭ኛ ዓመት ስንዘክር ከዚያ በፊት ለበርካታ ዘመናት ብራና ፍቀው፣ ቀለም ጨምቀው፣ ጽፈው፣ ተርጉመው ፣ ኢትዮጵያን ” ሃገረ መጻሕፍት ” ያሰኟትን ጠቢባንና ሊቃውንት ውለታ፤ እሳት ስንወራወር መጻሕፍቱ እንዳይቃጠሉ በቃል አጥንተው ፣ ዋሻ ተከተው ትውፊታችንን ያቖዩልንን ዐቃቢያነ ታሪክ ወሮታ አብረን መዘከራችን እንዳይዘነጋ ዐደራ ፡፡ ከዚያም ከጥንት ለመጡት ብቻ ሳይኾን ወደፊትም ለሚመጡት መጻሕፍት መኖሪያና መነበቢያ ያበጁትን ታላቅ መሪ የግ.ን.ነ. የቀዳማዊ ኃይለሥላሴን አባታዊ ስጦታ ከምስጋና ጋር እናስባለን ፡፡ በመጻሕፍት ብርሃን እንድናይ ለሚተጉ ኹሉ የዛሬው ብሔራዊ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት ኤጀንሲ የአክብሮት ምስጋናውን ያቀርባል፡፡
ይኩኖአምላክ መዝገቡ ዘርአብሩክ
Ethiopia Archives and Library Services, Ministry of Innovation and Technology, Balbbiys PLC, and Records Management Foundation for Africa (RMFA) are hosting the 40th RMFA Inte
የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት ሕዳር 13/2016 ዓ.ም ከደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ ጋር ዘላቂነት ያለው የጋራ የመግባቢያ ሠነድ ተፈራረመ፡፡
የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት ከኢትዮጵያን ሪድስ ጋር በመሆን "ጥራት ያለው የህፃናት የተረት መጽሐፍት ለህፃናት የግንዛቤ ክህሎት እድገት ያለው ሚና" በሚል ርዕሰ ጉዳይ የሳይንሳዊ ገለጻ እና ውይይት መርሐ ግብር ሕዳር 11/ 2016 ዓ.ም በዋቢ ሸበሌ ሆቴል
የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት በኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት ተጎበኘ፡፡
በአገራችን ኢትዮጵያ ለአስራ ስድስተኛ /16ኛ/ ጊዜ “የሰንደቅ አላማችን ከፍታ ለህብረ ብሔራዊ አንድነታችንና ሉአላዊነታችን ዋስትና ነው!” በሚል መሪ ቃል እየተከበረ የሚገኘውን የሰንደቅ ዓላማ ቀን ጥቅምት 5/2016 ዓ.ም በደማቅ ስነ ስርዓት አክብሯል፡፡
የኢትዮጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት ጥቅምት 1/2016 ዓ.ም ከለባዊ ዓለም ዓቀፍ ትምህርት ቤት ለመጡ የ3ኛ ክፍል ተማሪዎች ያዘጋጀውን የግማሽ ቀን የንባብ መርሐ ግብር አካሒዷል፡፡
የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት ሰነድና መዛግብትን ለማስተዳደርና ለማስወገድ በአዋጅ የተሰጠውን ስልጣንና ኃላፊነት ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችለውን የመማክርት ጉባኤ አቋቋሙ።
የተቋሙን ራዕይና ተልዕኮ እውን ሊያደርጉ የሚችሉ ሁለት ታላላቅ ስነዶች ተፈረሙ፡፡