የታዳጊ ልጆችን የንባብ ባህል ለማነቃቃት የሚረዳ የንባብ ቀን ተካሔደ ።
በኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት ከሜጀር ጀነራል ሐየሎም አርዓያ አንደኛ ደረጃ ት/ቤት የመጡ ተማሪዎች በተገኙበት የታዳጊ ልጆች የንባብ ባህልን ለማሳደግ የሚረዳ የንባብ ቀን ተካሔደ ።
የቤተመጻሕፍት ታሪክ የደግነት ታሪክ ነው ፡፡ ደጋግ ጸሐፍት በብዙ ትጋት ለአንክሮ፣ ለተዘክሮና ለአስተምህሮ የከተቡትን ክርታስ ሌሎች ደጋጎች በበኩላቸው ቤት ሰርተው ፣ መንበር አበጅተው ፣ ማቶት አብርተው ትውልዱ እንዲታደምላቸው ” እንካችኹ ይኽችን መጽሐፍ ብሉ ” ማለታቸው የሕብረተሰብ መሠረቱ ደግነት መኾኑን ያበስረናል ፡፡ የብሔራዊ ቤተመጻሕፍት ወመዘክርን ፸፭ኛ ዓመት ስንዘክር ከዚያ በፊት ለበርካታ ዘመናት ብራና ፍቀው፣ ቀለም ጨምቀው፣ ጽፈው፣ ተርጉመው ፣ ኢትዮጵያን ” ሃገረ መጻሕፍት ” ያሰኟትን ጠቢባንና ሊቃውንት ውለታ፤ እሳት ስንወራወር መጻሕፍቱ እንዳይቃጠሉ በቃል አጥንተው ፣ ዋሻ ተከተው ትውፊታችንን ያቖዩልንን ዐቃቢያነ ታሪክ ወሮታ አብረን መዘከራችን እንዳይዘነጋ ዐደራ ፡፡ ከዚያም ከጥንት ለመጡት ብቻ ሳይኾን ወደፊትም ለሚመጡት መጻሕፍት መኖሪያና መነበቢያ ያበጁትን ታላቅ መሪ የግ.ን.ነ. የቀዳማዊ ኃይለሥላሴን አባታዊ ስጦታ ከምስጋና ጋር እናስባለን ፡፡ በመጻሕፍት ብርሃን እንድናይ ለሚተጉ ኹሉ የዛሬው ብሔራዊ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት ኤጀንሲ የአክብሮት ምስጋናውን ያቀርባል፡፡
ይኩኖአምላክ መዝገቡ ዘርአብሩክ
በኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት ከሜጀር ጀነራል ሐየሎም አርዓያ አንደኛ ደረጃ ት/ቤት የመጡ ተማሪዎች በተገኙበት የታዳጊ ልጆች የንባብ ባህልን ለማሳደግ የሚረዳ የንባብ ቀን ተካሔደ ።
የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት (ወመዘክር) የዓለም የኦዲዮ ቪዥዋል ቅርሶች መታሰቢያ ዕለትን ጥቅምት 17/2018 ዓ.ም ከዩኔስኮ ጋር በመተባበር በተቋሙ አክብሯል።
በሀገር ደረጃ ለ18ኛ ጊዜ እየተከበረ የሚገኘው ብሔራዊ የሰንደቅ ዓላማ ቀን “ሰንደቅ ዓላማችን ለኢትዮጵያ ታላቅ የከፍታ ዘመን ብሥራት፣ ለብሔራዊ አንድነታችን፣ ለሉዓላዊነታችንና ለኢትዮጵያ ሕዳሴ!” በሚል መሪ ቃል የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት ከባሕልና ስፖር
መስከረም 20/2018.ዓ.ም ሣጃ ከተማ "የንባብ ሳምንት ለትምህርት ጥራት!"በሚል መሪ ቃል የየም ብሔረሰብ የዘመን መለወጫ "ሄቦ"በዓልን ምክንያት በማድረግ የኢትዮጵያ ቤተ- መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት፤ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ባህል ቱሪዝም ቢሮ፣ከየም ዞን
“መስከረም ተፈጥሮም ራሷን የምታድስ ከሆነ እኛም ቆም ብለን ራሳችንን ለማየትና ለመረዳት ጥሩ ጊዜ ነው፡፡”(የኢትዮጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አቶ ሠርፀ ፍሬስብሀት)
ጳጉሜ 3/2017 ዓ.ም ደቡብ አሪ ፤ ሸጲ የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት፣ የደቡብ ኢትዮጵያ ት/ት ቢሮ እና ወርልድ ቪዥን በአዘጋጅነት የተሳተፉበት "የንባብ ባህል ለት/ት ጥራት!" በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀው የንባብ ሳምንት የሚመለከታቸው የመንግ
ጷጉሜ 2/ 2017 ዓ.ም "የንባብ ባህል ለት/ት ጥራት!" በሚል መሪ ቃል በጂንካ ከተማ አንድነት ፓርክ የተሰናዳው የንባብ ሳምንት፣አውደርዕይ እና ተንቀሳቃሽ የሕፃናት ቤተ-መጻሕፍት በይፍ ተከፈተ።
ጷጉሜ 2/2017 ዓ.ም የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት ከሚመለከታቸው አጋር አካላት ጋር በመቀናጀት በመላ ኢትዮጵያ በመዘዋወር እያካሔደ የሚገኘው "የንባብ ባህል ለትምህርት ጥራት!" ንቅናቄ ዛሬ ጳጉሜ 2/2017ዓ.ም በጂንካ ማረማያ ፖሊስ ተቋም መካሔዱ