ታሪካዊ አውደ ርእይ ተዘጋጀ
የኢትዮጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት 82ተኛውን የአርበኞች የድል በዓል ምክንያት በማድረግ በተቋሙ ህንፃ ውስጥ በተዘጋጀ ስፍራ ሁነቱን የሚያሳዩ ፎቶ ግራፎችና መዛግብትን ለእይታ አደራጅቶ ከረቡዕ ሚያዝያ 25 /2015 ዓ.ም ጀምሮ ለተመልካች ክፍት አድርጓል።
የቤተመጻሕፍት ታሪክ የደግነት ታሪክ ነው ፡፡ ደጋግ ጸሐፍት በብዙ ትጋት ለአንክሮ፣ ለተዘክሮና ለአስተምህሮ የከተቡትን ክርታስ ሌሎች ደጋጎች በበኩላቸው ቤት ሰርተው ፣ መንበር አበጅተው ፣ ማቶት አብርተው ትውልዱ እንዲታደምላቸው ” እንካችኹ ይኽችን መጽሐፍ ብሉ ” ማለታቸው የሕብረተሰብ መሠረቱ ደግነት መኾኑን ያበስረናል ፡፡ የብሔራዊ ቤተመጻሕፍት ወመዘክርን ፸፭ኛ ዓመት ስንዘክር ከዚያ በፊት ለበርካታ ዘመናት ብራና ፍቀው፣ ቀለም ጨምቀው፣ ጽፈው፣ ተርጉመው ፣ ኢትዮጵያን ” ሃገረ መጻሕፍት ” ያሰኟትን ጠቢባንና ሊቃውንት ውለታ፤ እሳት ስንወራወር መጻሕፍቱ እንዳይቃጠሉ በቃል አጥንተው ፣ ዋሻ ተከተው ትውፊታችንን ያቖዩልንን ዐቃቢያነ ታሪክ ወሮታ አብረን መዘከራችን እንዳይዘነጋ ዐደራ ፡፡ ከዚያም ከጥንት ለመጡት ብቻ ሳይኾን ወደፊትም ለሚመጡት መጻሕፍት መኖሪያና መነበቢያ ያበጁትን ታላቅ መሪ የግ.ን.ነ. የቀዳማዊ ኃይለሥላሴን አባታዊ ስጦታ ከምስጋና ጋር እናስባለን ፡፡ በመጻሕፍት ብርሃን እንድናይ ለሚተጉ ኹሉ የዛሬው ብሔራዊ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት ኤጀንሲ የአክብሮት ምስጋናውን ያቀርባል፡፡
ይኩኖአምላክ መዝገቡ ዘርአብሩክ
የኢትዮጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት 82ተኛውን የአርበኞች የድል በዓል ምክንያት በማድረግ በተቋሙ ህንፃ ውስጥ በተዘጋጀ ስፍራ ሁነቱን የሚያሳዩ ፎቶ ግራፎችና መዛግብትን ለእይታ አደራጅቶ ከረቡዕ ሚያዝያ 25 /2015 ዓ.ም ጀምሮ ለተመልካች ክፍት አድርጓል።
መጻሕፍት ለዕውቀት ገበታ፣መዛግብትና የጽሑፍ ቅርሶች ለታሪክ ትውስታ በሚል መሪ ቃል የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት ከደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር መጋቢት 2/2015 ዓ.ም በተጀመረው የመጀመሪያው ዙር የመዛግብትና የጽሑፍ ቅርሶች ጉባዔ በደብረ ታቦር
መጻሕፍት ለዕውቀት ገበታ፣መዛግብትና የጽሑፍ ቅርሶች ለታሪክ ትውስታ በሚል መሪ ቃል የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት ከደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር መጋቢት 2/2015 ዓ.ም በተጀመረው የመጀመሪያው ዙር የመዛግብትና የጽሑፍ ቅርሶች ጉባዔ በደብረ ታቦር
መጻሕፍት ለዕውቀት ገበታ፣ መዛግብትና የጽሑፍ ቅርሶች ለታሪክ ትውስታ በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀው የመጀመሪያው የመዛግብትና የጽሑፍ ቅርሶች ጉባዔ እየተካሄደ ነው። የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት ከደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር ከመጋቢት 2-4/2015 ዓ
የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት አንድነት፣ጀግንነትና ጽናት በሚል መሪ ቃል ለ127ኛ ጊዜ የሚከበረውን የአድዋ ድል በዓል ከባህልና ስፖርት ሚኒስቴር እና ከመከላከያ ሚኒስቴር ጋር በመሆን የካቲት 21 ቀን 2015 ዓ.ም በመኮንኖች ክበብ በተከፈተው ታሪካዊ አውደር
የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት ከደቡብ ህዝቦች ብሔር ብሔረሰቦች ክልላዊ መንግስት ባህል ቱሪዝም ቢሮ ጋር በመተባበር በወላይታ ሶዶ ከተማ የካቲት 13 ቀን 2015 ዓ.ም በህዝብ ቤተ መጽሐፍት በነበረው የንባብ ክበባት ምስረታ መድረክ ላይ ለአራት አንደኛ ደረጃ
የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት ከደቡብ ህዝቦች ብሔር ብሔረሰቦች ክልላዊ መንግስት ባህል ቱሪዝም ቢሮ ጋር በመተባበር የካቲት 12 ቀን 2015 ዓ.ም በወላይታ ሶዶ ከተማ ማረሚያ ቤት የንባብ ልምድ ልውውጥ እና የመጽሐፍት ስጦታ መርሐግብር አከ
የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት ከደቡብ ህዝቦች ብሔር ብሔረሰቦች ክልላዊ መንግስት ባህል ቱሪዝም ቢሮ ጋር በመተባበር ከየካቲት 10 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ በዱራሜ ከተማ ባዘጋጀው የንባብ ክበባት ምስረታ እና አውደ ውይይት መርሐግብር ላይ አራት አንደኛ ደረጃ