• የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት/ወመዘክር
    ተጨማሪ ይመልከቱ
  • ወመዘክር የኦላይን አገልግሎት ፖርታል
    Integrated Library, Archive and Record Management System
    ተጨማሪ ይመልከቱ
  • ስለ ህትመተ ኢትዮጵያ የስራ ክፍል እናስተዋውቆት!
    ተጨማሪ ይመልከቱ
  • መዛግብትና የጽሑፍ ቅርሶች ለጥናትና ምርምር
    መዛግብትና የጽሑፍ ቅርሶች ለጥናትና ምርምር
    መዛግብትና የጽሑፍ ቅርሶች ለጥናትና ምርምር
  • ወመዘክር እግር ኳስ ክለብ
    ወመዘክር ስፖርት 2015 ዓ.ም.
    ተጨማሪ ይመልከቱ
  • የኢትዮጵያ የዘመን አቆጣጠር ቀመር አቡሻኸር
    የኢትዮጵያ የዘመን አቆጣጠር ቀመር አቡሻኸር
  • ፍትኃ ነገሥት (በ19ነኛው ክፍለ ዘመን የተጻፈ)::
    ኢትዮጵያ በዩኔስኮ ካስመዘገበቻቸው የጽሑፍ ቅርሶች አንዱ የሆነውና በተቋማችን የሚገኘው
    ፍትኃ ነገሥት
  • መጽሐፈ ተፍሢር
    በተቋማችን ከሚገኙ ጥንታውያን የብራና መጽሐፍት ክምችት የተወሰደ
    መጽሐፈ ተፍሢር
  • ግርማዊ ጃንሆይ ባልጋ ወራሽነታቸው ዘመን
    በኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት በሕትመት አትዮጵያ የስራ ክፍል ከሚኙ ክምችቶቻችን
    ግርማዊ ጃንሆይ ባልጋ ወራሽነታቸው ዘመን
  • መጽሀፈ ቅዱስ ቁራን በ18ኛው መቶ ክፍለ ዘመን
    መጽሀፈ ቅዱስ ቁራን በ18ኛው መቶ ክፍለ ዘመን

አቶ ይኩኖአምላክ መዝገቡ

የቤተመጻሕፍት ታሪክ የደግነት ታሪክ ነው ፡፡ ደጋግ ጸሐፍት በብዙ ትጋት ለአንክሮ፣ ለተዘክሮና ለአስተምህሮ የከተቡትን ክርታስ ሌሎች ደጋጎች በበኩላቸው ቤት ሰርተው ፣ መንበር አበጅተው ፣ ማቶት አብርተው ትውልዱ እንዲታደምላቸው  ” እንካችኹ ይኽችን መጽሐፍ ብሉ ” ማለታቸው የሕብረተሰብ መሠረቱ ደግነት መኾኑን ያበስረናል ፡፡ የብሔራዊ ቤተመጻሕፍት ወመዘክርን ፸፭ኛ ዓመት ስንዘክር ከዚያ በፊት ለበርካታ ዘመናት ብራና ፍቀው፣ ቀለም ጨምቀው፣ ጽፈው፣ ተርጉመው ፣ ኢትዮጵያን ” ሃገረ መጻሕፍት ” ያሰኟትን ጠቢባንና ሊቃውንት ውለታ፤ እሳት ስንወራወር መጻሕፍቱ እንዳይቃጠሉ በቃል አጥንተው ፣ ዋሻ ተከተው ትውፊታችንን ያቖዩልንን ዐቃቢያነ ታሪክ ወሮታ አብረን መዘከራችን እንዳይዘነጋ ዐደራ ፡፡ ከዚያም ከጥንት ለመጡት ብቻ ሳይኾን ወደፊትም ለሚመጡት መጻሕፍት መኖሪያና መነበቢያ ያበጁትን ታላቅ መሪ የግ.ን.ነ. የቀዳማዊ ኃይለሥላሴን አባታዊ ስጦታ ከምስጋና ጋር እናስባለን ፡፡ በመጻሕፍት ብርሃን እንድናይ ለሚተጉ ኹሉ የዛሬው ብሔራዊ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት ኤጀንሲ የአክብሮት ምስጋናውን ያቀርባል፡፡

 

ይኩኖአምላክ መዝገቡ ዘርአብሩክ

 


ተከተሉኝ
አቶ ይኩኖአምላክ መዝገቡ

ዜና

ወመዘክር / Wemezeker / ኦን ላይን የአገልግሎት ድህረገጽ

የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት የተቀናጀ የቤተመጻሕፍት ፣ የመዛግብትና የሪከርድ አስተዳደር ስርዓት

ማስታወቂያ

አጋሮች