የንባብ ክበባት ምሥረታ የግንዛቤ ማስጨበጫ የምክክር መድረክ ተደረገ።
የኢትዩጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት በደሴ ከተማ የትምህርት ቤቶች የንባብ ክበባት ምሥረታ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ መርሐ ግብር በደሴ ከተማ አካሒዷል።
የቤተመጻሕፍት ታሪክ የደግነት ታሪክ ነው ፡፡ ደጋግ ጸሐፍት በብዙ ትጋት ለአንክሮ፣ ለተዘክሮና ለአስተምህሮ የከተቡትን ክርታስ ሌሎች ደጋጎች በበኩላቸው ቤት ሰርተው ፣ መንበር አበጅተው ፣ ማቶት አብርተው ትውልዱ እንዲታደምላቸው ” እንካችኹ ይኽችን መጽሐፍ ብሉ ” ማለታቸው የሕብረተሰብ መሠረቱ ደግነት መኾኑን ያበስረናል ፡፡ የብሔራዊ ቤተመጻሕፍት ወመዘክርን ፸፭ኛ ዓመት ስንዘክር ከዚያ በፊት ለበርካታ ዘመናት ብራና ፍቀው፣ ቀለም ጨምቀው፣ ጽፈው፣ ተርጉመው ፣ ኢትዮጵያን ” ሃገረ መጻሕፍት ” ያሰኟትን ጠቢባንና ሊቃውንት ውለታ፤ እሳት ስንወራወር መጻሕፍቱ እንዳይቃጠሉ በቃል አጥንተው ፣ ዋሻ ተከተው ትውፊታችንን ያቖዩልንን ዐቃቢያነ ታሪክ ወሮታ አብረን መዘከራችን እንዳይዘነጋ ዐደራ ፡፡ ከዚያም ከጥንት ለመጡት ብቻ ሳይኾን ወደፊትም ለሚመጡት መጻሕፍት መኖሪያና መነበቢያ ያበጁትን ታላቅ መሪ የግ.ን.ነ. የቀዳማዊ ኃይለሥላሴን አባታዊ ስጦታ ከምስጋና ጋር እናስባለን ፡፡ በመጻሕፍት ብርሃን እንድናይ ለሚተጉ ኹሉ የዛሬው ብሔራዊ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት ኤጀንሲ የአክብሮት ምስጋናውን ያቀርባል፡፡
ይኩኖአምላክ መዝገቡ ዘርአብሩክ
የኢትዩጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት በደሴ ከተማ የትምህርት ቤቶች የንባብ ክበባት ምሥረታ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ መርሐ ግብር በደሴ ከተማ አካሒዷል።
የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት ከወሎ ዩኒቨርሲቲ እና ከአማራ ክልል ባህል ቱሪዝም ቢሮ ጋር በመተባበር ስምንተኛውን አገር አቀፍ የግእዝ ጉባዔ "ናዝልፍ ኀበ አንብቦተ መጻሕፍተ ግእዝ" በሚል መሪ ቃል በደሴ ከተማ በወሎ ዩኒቨርሲቲ የመጀመሪያ ቀን ጉባዔ
ለሀገር እና ለኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና መጻሕፍት አገልግሎት (ወመዘክር) ታላቅ ባለውለታ ለሆኑት ለብላታ መርስዔ ኀዘን ወልደ ቂርቆስ ልጃቸው አቶ አምኃ መርስዔ ኀዘን ወልደ ቂርቆስ እና ወዳጅ ቤተሰባቸው እንዲሁም የሚድያ አካላት በተገኙበት የእውቅና መስጠት መርሐ ግብር ተከናውኗ
በኢትዮጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች አካቶ ትግበራ ስራ አስፈፃሚ የተዘጋጀው ሴቶችን የማብቃትና የአካቶ ትግበራ ስልጠና ለተቋሙ ባለሙያዎች ተሰጠ::
የአዳራሽ መድረኩን ደረጃውን በጠበቀ መልኩ ለማደስ ስምምነቱ የተፈረመው በኢትዮጵያ ቤተመዛግብት እና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት እና በአቶ አምኃ መርስዔ ኀዘን ወልደ ቂርቆስ መካከል ሲሆን ስምምነቱንም የአገልግሎቱ የጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አባተ ካሳው እና የብላታ መርስዔ ኀዘን ወልደ ቂ
የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት በምዕራብ ኦሞ ዞን ለሚገኙ 12 ት/ቤቶች፣ 1 የሕህዝብ ቤተ-መጻሕፍትና በዞኑ ለሚገኘው የቱም ማረሚያ ቤት 863,791 ብር ዋጋ ያላቸውን 2800 መጻሕፍት በስጦታ አበርክቷል፡፡
የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ባህል፣ ቱሪዝምና ስፓርት ቢሮ ጋር በመተባበር ከመጋቢት 1/2017 ዓ.ም ጀምሮ “ማንበብ በጥበብ ጎልብቶ ለማበብ!” በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀው የንባብ ሳምንት እና አውደ ውይይት መድረ
የኢትዮጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት በሰነድና መዛግብት አስተዳደር ለ43 ጸሐፊዎች እንዲሁም የአሰልጣኞች ስልጠና ለአምስት ወንድ እና ለስምንት ሴት በድምሩ ለሃምሳ ስድስት ሰልጣኞች ስልጠና በመስጠት የካቲት 28/ 2017 ዓ.ም አስመርቋል፡፡