ከ800ሺ ብር በላይ ዋጋ ያላቸው መጻሕፍት በስጦታ ተበረከቱ
የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት በምዕራብ ኦሞ ዞን ለሚገኙ 12 ት/ቤቶች፣ 1 የሕህዝብ ቤተ-መጻሕፍትና በዞኑ ለሚገኘው የቱም ማረሚያ ቤት 863,791 ብር ዋጋ ያላቸውን 2800 መጻሕፍት በስጦታ አበርክቷል፡፡
የቤተመጻሕፍት ታሪክ የደግነት ታሪክ ነው ፡፡ ደጋግ ጸሐፍት በብዙ ትጋት ለአንክሮ፣ ለተዘክሮና ለአስተምህሮ የከተቡትን ክርታስ ሌሎች ደጋጎች በበኩላቸው ቤት ሰርተው ፣ መንበር አበጅተው ፣ ማቶት አብርተው ትውልዱ እንዲታደምላቸው ” እንካችኹ ይኽችን መጽሐፍ ብሉ ” ማለታቸው የሕብረተሰብ መሠረቱ ደግነት መኾኑን ያበስረናል ፡፡ የብሔራዊ ቤተመጻሕፍት ወመዘክርን ፸፭ኛ ዓመት ስንዘክር ከዚያ በፊት ለበርካታ ዘመናት ብራና ፍቀው፣ ቀለም ጨምቀው፣ ጽፈው፣ ተርጉመው ፣ ኢትዮጵያን ” ሃገረ መጻሕፍት ” ያሰኟትን ጠቢባንና ሊቃውንት ውለታ፤ እሳት ስንወራወር መጻሕፍቱ እንዳይቃጠሉ በቃል አጥንተው ፣ ዋሻ ተከተው ትውፊታችንን ያቖዩልንን ዐቃቢያነ ታሪክ ወሮታ አብረን መዘከራችን እንዳይዘነጋ ዐደራ ፡፡ ከዚያም ከጥንት ለመጡት ብቻ ሳይኾን ወደፊትም ለሚመጡት መጻሕፍት መኖሪያና መነበቢያ ያበጁትን ታላቅ መሪ የግ.ን.ነ. የቀዳማዊ ኃይለሥላሴን አባታዊ ስጦታ ከምስጋና ጋር እናስባለን ፡፡ በመጻሕፍት ብርሃን እንድናይ ለሚተጉ ኹሉ የዛሬው ብሔራዊ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት ኤጀንሲ የአክብሮት ምስጋናውን ያቀርባል፡፡
ይኩኖአምላክ መዝገቡ ዘርአብሩክ
የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት በምዕራብ ኦሞ ዞን ለሚገኙ 12 ት/ቤቶች፣ 1 የሕህዝብ ቤተ-መጻሕፍትና በዞኑ ለሚገኘው የቱም ማረሚያ ቤት 863,791 ብር ዋጋ ያላቸውን 2800 መጻሕፍት በስጦታ አበርክቷል፡፡
የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ባህል፣ ቱሪዝምና ስፓርት ቢሮ ጋር በመተባበር ከመጋቢት 1/2017 ዓ.ም ጀምሮ “ማንበብ በጥበብ ጎልብቶ ለማበብ!” በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀው የንባብ ሳምንት እና አውደ ውይይት መድረ
የኢትዮጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት በሰነድና መዛግብት አስተዳደር ለ43 ጸሐፊዎች እንዲሁም የአሰልጣኞች ስልጠና ለአምስት ወንድ እና ለስምንት ሴት በድምሩ ለሃምሳ ስድስት ሰልጣኞች ስልጠና በመስጠት የካቲት 28/ 2017 ዓ.ም አስመርቋል፡፡
በኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት የአብያተ መጻሕፍት መረጃ ሀብቶች አስተዳደር መሪ ስራ አስፈጻሚ አቶ ስለሺ ሽፈራው እንደተናገሩት ከአራት ሺህ በላይ ያገለገሉ መጽሐፍት ከኢትዮ ቴሌኮም በቀን 27/2017 ዓ.ም ለተቋሙ በስጦታ መበርከቱን ተናግረዋል፡፡
ሙስናን በሚመለከት የዜግነት ግዴታዬን እወጣለሁ! በሚል መሪ ቃል የተከበረውን የጸረ ሙስናን ቀን ምክንያት በማድረግ የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ከተጠሪ ተቋማት በጋራ በመሆን በሙስናና ብልሹ አሰራር ዙሪያ የሚታዩ ክፍተቶችን ለመከላከል የሚያስችል ሶስተኛው ዙር የግንዛቤ ማስጨበጫ
የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት (ወመዘክር) በወር ቅብብሎሽ የሚያዘጋጀው የወር ወንበር የተሰኘው መርሐግብር በወርሀ የካቲት በዕለተ ቅዳሜ በቀን 22/2017 ዓ.ም በተቋሙ የብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደስላሴ አዳራሽ የወሩ ወንበር ተዘርግቷል።
የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሴቶችና ህፃናት ማህበራዊ ጉዳዮች ቢሮ ስር በሚተዳደረው የአካል ጉዳተኞች ተሃድሶ ልማት ማዕከል ቤተ-መጻሕፍት አደራጅቶ አስመርቋል፡፡
የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት ከማይንግሰንግ የህክምና ኮሌጅ 50 ሺ ብር የሚያወጡ 138 መጻሕፍትን በስጦታ ተረክቧል፡፡