ዋና ዳይሬክተር
“አንድ ሀገር÷ ያለፈውን ታሪኩን እንደ አጥንቱ፣የአሁኑን ኹኔታ እንደ ሥጋው፣ የወደፊቱን ተስፋውን ደግሞ እንደ መንፈሱ አድርጎ የሚመለከት ነው።ይህ አመለካከቱ ጠንካራ ኾኖ እንዲቀጥል÷ የተረት እና የታሪክ፣ የስሜት እና የኅሊና፣ የዐዲስ እና የአሮጌ፣ የወጣት እና የአረጋዊ፣ እንዲሁም የእምነት እና የዕውቀት መስማማት የግድ ያስፈልገዋል። እነዚህ በመጀመሪያ ሲታዩ የተራራቁ የሚመስሉ ጠባያት እና ባሕርያት÷ በአንድ ማሕቀፍ ውስጥ ተጋምደው የሀገርን የዕድገት ጉዞ መምራት ሲችሉ÷ሀገርን በውል መረዳት ይቻላል። ይህንን ግንዛቤ ለማዳበር እና የዓለማቱን መስተጋብር ለመረዳት ትልቁ መሣሪያ ደግሞ ንባብ ነው።”
ሠርፀ ፍሬስብሐት
የኢትዮጵያ ቤተመዛግብት እና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት (ወመዘክር) ዋና ዳይሬክተር